Home » Sunday sermon – March 30, 2025

ከመንፈስ ቅዱስ ጋር መተዋወቅ ያስፈልገናል

Last updated on March 30, 2025 - by Pastor Tariku Eshetu

ትምህርት ሶስት:- የአምልኮና የምስጋና ድባብን ማሳደግ

መግቢያ

ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ለመተዋወቅ ልናደርገው የሚገባን ምንድ ነው የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ባለፈው ሳምንት የእግዚአብሔርን ቃል ማሰላሰልና በፀሎት የመትጋትን አስፈላጊነት ተመልክተን ነበር።በዛሬው ትምህርት ደግሞ የአምልኮና የምስጋና ድባብን የማሳደግ አስፈላጊነትን እንመለከታለን።

1: አምልኮ ምንድ ነው? ዮሐ 4:23-24, ሮሜ12:1, ዕብ13:15

1:1 ትርጉም/ብይን:- እግዚአብሔርን በማንነቱ ማምለክና ልብን ለእርሱ አሳልፎ መስጠት ነው።
1:2 መዝሙሮችን መዘመር ብቻ ሳይሆን እርሱን በመታዘዝ፣በማክበር እና በመውደድ መኖር ነው።
1:3 የምናደርገውን ሁሉ ለእግዚአብሔር ክብር ማድረጋችንን እርግጠኛ መሆን ነው።
1:4 አምልኮ በመንፈስ መመራትና በእውነት የተሞላ መሆን አለበት።
1:5 አምልኮ ነፍስን ለእግዚአብሔር መስዋእት አድርጎ መስጠት ነው።
1:6 አምልኮ ለእግዚአብሔር የማያቋርጥ የምስጋና መስዋዕት ማቅረብ ነው።

2: የአምልኮ መገለጫዎች:-

2:1 መዝሙር መዘመር። መዝ 95:1-2,ኤፌ5:19;መዝ 100:4-5
2:2 ሁል ጊዜ ሰለ ሁሉ እግዚአብሔርን ማመስገን
2:3 ለቸርነቱ፣ለታማኝነቱና ለኃይሉ እግዚአብሔርን ማክበር።

3: የአምልኮና የምስጋና ድባብ ሲኖር:- ሐዋ13:1-4

3:1 መንፈስ ቅዱስ ይናገራል
3:2 ሰውች ለአገልግሎት በቤ/ክ ይለያሉ
3:3 ሰወች በመንፈስ ቅዱስ ለወንጌል ይላካሉ።

ማጠቃለያ

አማኞች ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በጥልቀት ሊተዋወቁ እንደሚገባቸው የአዲስ ኪዳን ትምህርት ነው። ያለእርሱ አማኞች ምንም መሆንም ማድርግም አይችሉምና። ስለዚህ በመንፈስ ቅዱስ ጋር በጥልቀት ለመተዋወቅ የአምልኮና የምስጋና ድባብ በመካከላችን ሊኖር ይገባል። ለዝህም እያንዳንዱ አማኝ የአምልኮን ምንነት ማውቅ፣ የአምልኮን መገለጫዎች ማወቅና ማምለክ እንዲሁም በአምልኮ ውስጥ ለሚመጣው የመንፈስ ቅዱስ ድምፅ መታዛዝ ያስፈልገዋል።ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ለመተዋወቅ የአምልኮና የምስጋናን ድባብ እናሳድግ!!!!!!!!!!!!

Source: https://cmaeec.com/w...

the cross
Jesus is Lord
John 3:16

Whoever believes in him shall not perish but have eternal life.