Home » Sunday sermon – May 18, 2025

ለጥሪያችን እንኑር!!!

Last updated on May 18, 2025 - by Pastor Tariku Eshetu

ንባብ ኤፌ 4:1-16

ዓላማ

አማኞች ለተቀበሉት ጥሪ የሚመጥን ኑሮ እንዲኖሩ ማሳሰብ።
አማኞች የአገልግሎት ስጦታዎችን እንዲጠቀሙ ማበረታት።
አማኞች ለመንፈሳዊ እድገት ተገቢውን ትኩረት እንዲሰጡ ማሳሰብ።

መግቢያ

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ደብዳቤው የመጀመሪያ ክፍል ላይ ነገረ ድህነትን በተመለከት ዝርዝር ጉዳዮችን ከፃፈ በኃላ፣ በቀጣይነት ለዳነው ሰው እንዲህ ብሎ ጥሪ ያቀርባል “ለተቀበላችሁት ጥሪ ተገቢውን ኑሮ እንድትኖር እለምናለሁ” የሚል ተማፅኖን ያሰማል። በቀጣይነትም እንዴት መኖር እንደሚገባ ዝርዝር ትምህርት ያስተምራል ከነዚህ ትምህርቶች የወሰኑትን በዚህ ጊዜ እንመለከታለን።

1: ጥሪያችንን በመረዳትና የመንፈስን አንድነት በመጠቅ እኑር። ኤፌ 4:1-6

1:1 ጥሪያችንን በመረዳት እንኑር።

1:1:1 ለዚህ ኑሮ የጠራን ጌታ ነው።
1:1:2 ጥሪው እኛ ጋር እንዲደርስ ዋጋ ተከፍሎበታል።
1:1:3 ጥሪው ትሁት፣የዋህና ታጋሽ መሆን ይጠይቃል።

1:2 የመንፈስን አንድነት በመጠበቅ እንኑር።

1:2:1 ውደ አንድ ተስፋ ስለተጠራን።
1:2:2 አንድ አካል ስለተደርግን።
1:2:3 በሁላችን ውስጥ አንድ መንፈስ ስላለ።
1:2:4 የሁላችን ጌታ አንድ ስለሆነ።
1:2:5 አንድ እምነትና አንድ ጥምቀት ስላለን።
1:2:6 በሁላችን የሚሰራ አንድ አባት ስላለን።

2: የአገልግሎት ስጦታዎችን በመቀበል እንኑር። ኤፌ 4:7-13

2:1 የክርስቶስ ሞት፣መቅበር፣መነሳትና መክበር ውጤቶች ስለሆኑ።
2:1 ስጦታዎች የተስጡት በአላማና በምክንያት ስለሆነ።
2:3 የእግዚአብሔርን ልጅ በማመንና በማውቅ ወደሚገኘው አንድነት ስለሚያደርሱን።

3: በመንፈሳዊ እድገትናብስለት እኑር። ኤፌ4:14-16

3:1 ለልዩ ልዩ የትምህርት ነፋስ እንዳንጋለጥ።
3:2 በሰወች ረቂቅ ተንኮል እንዳንታለል።
3:3 እውነትን በፍቅር መናገር እንድንችል።
3:4 በነገር ሁሉ ወደ ክርስቶስ ለማደግ።
3:5 እርስ በርስ ተያይዘን ለመስራትና በፍቅር እንድናድግ።

ማጠቃለያ

ክርስትና አንድ የታወቀ የሀይማኖት መሪ የመሰረተው ሀይማኖት አይደለም።ነገር ግን እግዚአብሔር በልጁ ሞት፣ መቀበር፣መነሳትና መክብር ምክንያት ሰወች የኃጢአት ይቅርታ እንዲቀበሉ ለቀረበላቸው አምላካዊ ጥሪ በእምነት ምላሽ የሰጡ ሰወች አንድነት እንጂ። ስለዚህ ይህን ጥሪ የተቀበሉ ሁሉ ደግሞ ለጥሪው የሚመጥን ኑሮ እንዲኖሩ ግዴታ አለባቸው። ስለዚህ ለጥሪያችን የሚመጥነውን ኑሮ በቃሉ መስፈርት እኑር።

Source: https://cmaeec.com/w...

the cross
Jesus is Lord
John 3:16

Whoever believes in him shall not perish but have eternal life.