Home » Sunday sermon – February 23, 2025

በመንፈስ የእግዚአብሔርን ጥበብ ማግኘት

Last updated on February 23, 2025 - by Pastor Tariku Eshetu

ክፍል ሁለት:- የፍጥረታዊና የመንፈሳዊ ሰው ልዩነትን ማወቅ።

የንባብ ክፍል:- 1ቆሮንቶስ 2:14-16

ዓላማ

-በፍጥረታዊውና በመንፈሳዊው ሰው መካከል ያለውን ልዩነት በቃሉ ማሳየት።
-እውነተኛው መንፈሳዊነት መፀሀፍ ቅዱሳዊ እንደሆነ ማረጋገጥ።
-የእግዚአብሔርን ጥበብ ማግኘት ለእነተኛው መንፈሳዊ ሰው ብቻ እንደሆነ ማረጋገጥ።

መግቢያ

የእግዚአብሔር ጥበብ ከዚህ ዓለም ጥበብ የተለየ እና የዚህ አለም ግዥዎች የማያውቁት መሆኑን፤እንዲሁም እግዚአብሔር ለሚወዱት በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት የሚሰጣቸው መሆኑን ተምረን ነበር።በዛሬው ትምህርት ደግሞ ይህን በመንፈስ ቅዱስ የሚሰጠውን የእግዚአብሔር ጥበብ ማን መቀበል እንደሚችል እንመለከታለን።

1: የፍጥረታዊውና የመንፈሳዊው ሰው ልዩነት ምንድ ነው?። 1ቆሮ 2:14-16

1:1 የፍጥረታዊው ሰው መለያዎች ምንድ ናቸው?

1:1:1 መንፈስ ቅዱስ የለውም።
1:1:2 ከመንፈስ ቅዱስ የሆነውን ነገር መቀበል አይችልም።
1:1:3 ከመንፈስ ቅዱስ የሆነው ነገር ለርሱ ሞኝነት ነው።
1:1:4 ከመንፈስ ቅዱስ የሆነውን ነገር አይገነዘብም።

1:2 የመንፈሳዊው ሰው መለያዎች

1:2:1 መንፈስ ቅዱስ አለው።
1:2:2 በመንፈስ ቅዱስ የመንፈስ ቅዱስን ነገር ይመረምራል።
1:2:3 እርሱ በማንም አይመረመርም።
1:2:4 የክርስቶስ ልብ/አዕምሮ አለው።

2: መንፈሳዊነት ምንድ ነው?

2:1 በክርስቶስ ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ጋር መግናኘት ነው። ዮሐ 14:6
2:2 በመንፈስ ቅዱስ ኃይል መሞላት ነው። ሐዋ ሉቃ 24:49, ሐዋ1:8
2:3 በቅዱስ ቃሉ መመራት ነው።መዝ 119:105,9
2:4 በአእምሮ መታደስ መለወጥ ነው። ሮሜ 12:2
2:5 በመታዘዝ የሚገለጥ እምነት ነው።ያዕ 2:14

ማጠቃለያ

የእግዚአብሔርን ጥበብ በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት ለመቀበል መንፈሳዊ ስው መሆን ይጠይቃል።ስለዚ መንፈሳዊ ሰው ለመሆንና የእግዚአብሔርን ጥበብ በመንፈስ ቅዱስ ለመቀበል በፍጥረታዊውና በመንፈሳዊ ሰው መካከል ያለውን ልዩነት በቃሉ መሰረት መለየት እና በመንፈሳዊነታችን ላይ እርግጠኛ መሆን ይጠይቅል። በቀጣይነትም ወደ እውነተኛውና መፀሐፍ ቅዱሳዊ ወደሆነው መንፈሳዊነት በቃሉ መሰረት መግባት ያሰፈልግል። ይህን በተመለከተ ሳምንት እንማራልን።

Source: https://cmaeec.com/w...

the cross
Jesus is Lord
John 3:16

Whoever believes in him shall not perish but have eternal life.